ไม่สามารถเล่นวิดีโอนี้
ขออภัยในความไม่สะดวก

በድጋሚ እና ቀሪ ምርጫ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁለት የፓርላማ መቀመጫ አሸነፉ

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 7 ก.ค. 2024
  • በሰኔ ወር አጋማሽ በአራት ክልሎች በተካሄደው “ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ”፤ ሁለት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁለት የፓርላማ መቀመጫ አሸነፉ። በባለፈው ጠቅላላ ምርጫ ያልተደረገባቸውን አብዛኞቹን የክልል ምክር ቤት እና የፓርላማ መቀመጫዎች፤ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል።
    በአፋር፣ ሶማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16፤ 2016 በተካሄደው “ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ”፤ 12 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና 12 የግል ዕጩዎች እንደተሳተፉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። በዚሁ ምርጫ ዘጠኝ የፓርላማ እና የ108 የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ለውድድር ቀርበዋል።
    ሶስት የፓርላማ መቀመጫዎች ለምርጫ በቀረቡበት በአፋር እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች፤ ሁሉንም ያሸነፈው ብልጽግና ፓርቲ መሆኑን ምርጫ ቦርድ ትላንት ቅዳሜ ሰኔ 29፤ 2016 ይፋ ያደረገው ውጤት አመልክቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውድድር ከተደረገባቸው ስድስት የፓርላማ መቀመጫዎች፤ አራቱን ያሸነፈው ገዢው ፓርቲ መሆኑንም ቦርዱ አስታውቋል።(ኢትዮጲያ ኢንሳይደር)
    ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
    -------------------------------------------------------------------------------------------
    የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
    ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
    ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
    ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
    ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
    ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

ความคิดเห็น •