Eniam sle esa bebesmatea des blognal ye Enate yagot leji nechi besm enji beakal anawukatm neber gn lealochun Eht wondma gar slemngenagni bezna ynegrun neber❤
Oh my Hod , my childhood memory. I grew up up listening to about Aualnesh Simone. I used to scare when my family talk about her , they talk very silently with fear , like she was not visible, I didn’t think she was a living human , b/c I was a child
😂😂❤ ye Ehapa tori ke 1970- 1983 meritalech bilalech Zegabiwa ke 1970 ke ahun 2016 46 amet honuwal keteweledech woyim tori memirat be sint ametuwa yihon yejemerechiwu ...... be gimit 20 amet bihon tori meri yehonechiwu 20+46 = 66 ametuwa yihonal be gimit
ይህን ታሪክ በአጋጣሚ ሳየው በአያልነሽ ስም በ1982ዓ/ም በደርግ ታጣቄወች አና ፖሊሶች ተደብድቤ እስር ቤት ገብቸ ነበር ምክንያቱም እንዲህ ነበር የኔ ትልቅ እህት ስሟ አያልነሽ ቢያዝን ትባላለች መልኳም እሷን ትመሰላለች በአጋጣሚ እህቴ ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ እኔ ለእሷ የአውቶቡስ ትኬት ለመቁረጥ በሄድኩበት ስዐት አያልነሽ ወንበዴ ናት ተብየ ብዙ ፍዳ አይቻለሁ በአጋጣሚ ይህን ታሪክ ስዳምጥ ትዝ አለኝ የባህር ዳር ልጅ ነኝ
የአያልነሽን በሕይወት መኖር በመስማቴ ደስ ብሎኛል ❤😂❤
እውነት ነው አያልነሽ ድሮ በልጅነት በጅግነት የሚውራልት ሴት ናች።
የአያልነሽ በህይወት መኖር እጅግ ደስ ብሎኛል አብረን ለአመታት ታግለናል የትግል ስሞ አያልነሽ ይሁን እንጂ ትግል ላይ እያለን ጎርዴ በሚል ስም ትጠራ ነበር እኔ የትግል ስሜ በቀለ እባል ነበር አያልነሽ በህይወት በመኖሮዋ እጅግ ደስ ብሎኛል በማንኛዉም መንገድ ባገኛት እና ባዋራት ደስ ይለኛል ለብዙ አመታት አብራኝ የነበረች የሴት ጀግና የነበረች ነቺ፣
Eniam sle esa bebesmatea des blognal ye Enate yagot leji nechi besm enji beakal anawukatm neber gn lealochun Eht wondma gar slemngenagni bezna ynegrun neber❤
የአያልነሽ አባት የአያቴ ወንድም ሲሆን ስማቸዉም ከበደ ጥሩነህ ሀይሉ ገዛኸኝ አበራ ነዉ። ትዉልዳቸዉ ትግራይ አድዋ እንዳየሱስ ቢሆንም በንግድ ምክንያት ወደ ጎንደር ታላቅ ወንድሙ አያቴ ሲመጣ እሱም ተከትሎት መጣ እናም ጎንዴሬዎቹን አግብተዉ እዛዉ ልጆችን አፍርተዉ ቀሩ ከአያቴ ዉጪ ሁለት ወንድሞች ወይም አጎቶች ነበሯት። ሙሉነህ ጥሩነህ እና ብርሃኔ ጥሩነህ። እናቷም ወለላዬ ነፍሳቸዉን ይማር እና መልካም እናት ነበሩ❤🙏🙏❤እናም ሌላዉ ነገር ደግሞ አባቷ በየትኛዉም የመንግስት እጅ አልተገደሉም በተፈጥሮ በእግዚአብሔር ጥሪ ነዉ የሄዱት
😮ደንቅ ነው🙏
❤❤❤ እናመሰግናለን የቤተሰብ ታሪክ ነው በጣም ደስ ብሎኛል በሰጠሽው በቂ መልስ
ከበደ ጥሩነህ ሀይሉ ገዛኸኝ አበራ yemibal Tigre demo keyet new yemetaw? Abet wushet, yetarik shimiya 😕
@@yeshibelay9418 በእዉነቱ ከሆነ ምላሽ መስጠት አይጠበቅብኝም ነገር ግን ለመዋሸትም ምንም ምክንያት የለኝም እናም ምን አልባ ይህን የማየት እድል ካላት በበረሀ ስሟ አያልነሽ በቤት ስሟ አለምገዥ ከበደ እዉነት ወይም ዉሸት መሆኑን እሷ እራሷ ትመልስልናለች። መልካም ቀን አመሰግናለሁ🙏
በዚህ ስም ዉስጥ ገብረ የሚል ስም አለ እንዴ…..ነዉ ወይስ በዚህም እኛ ነን…. መሆኑ ነዉ…..ወይ ክፉ ልክፍት…ለማንኛዉም ወያኔም ሆነ ሌላዉ ከሚወድሳቸዉ ሴት ታጋይ ከሚላቸዉ ከንቱዎች ይልቅ የዚህች ጀግና ታሪክ ሪከርዱን የሰቀለ/ተወዳዳሪ የማይገኝለት ነዉ ፤፤
What a girl ? She is like Billy the kid in Texas true legend. The Lone Ranger. What a Fano she was lovely story
አያልነሽ
ዕድሜዋ ከ50 ይበልጣል
50 አመት እማ እኛንም ጎሸመን የኔ እልም በጣም ትልቅ ናት
እዉነትህን እኔ ሀምሳ አልፌዋለሁ ከልጅነት ጀምሮ ነው እየሰማኋት ያደግሁት ከ60 አመታት በላይ ናት በትክክል።
የዕድሜ ጉዳይ ስህተት አለው 1966 ተወለደች አሉ ከዛም ወንድሟ እስክንድር ከበደ ስልጣን ከሰጣቸው 1969ነበር አሉ :: የተምታታ ነው እኔ ከራሴ(1956) 60ገብቻለሁ ገና 22ዓመት ነበር ቁንዝላ ልደባለቃት የሄድኩት እሱ በዛ ጊዜ ከቋራ ወደዚህ እያፈገፈጉ የመጡበት ጊዜ ነበር በዛ ጊዜ 32እንኳን ብትሆን አሁን በትንሹ 70 ይሆናታል ወያኔ ከገባ እኮ 33ዓመት ሆኖታል እሱ ከዛ በፊት ከደርግ ጋ ስትዋጋ የነበረች ናት
እኔ አያልነሽን ታሪከ እኔ አውቃለው። በፍኖተ ሰላም ስሜነደስታ ሲፈለጉ እኛ ስንጠየቅ ነበር አበረኢማም አውቃለሁ አያልነሽ በሰላም በመኖሯ በጣም ደስ ይላላ እባክዎት ሰላምታ አቅርቡልኝ ።
50 አመት እድሜዋ ትክክል ሊሆን ኡይችልም።
አብዮቱም 50 አመቱ ነው ,20219 _1966,
አያልነሽ ስሜነህ የጎጃሙ ገዢ የቀኝአዝማች ስሜነህ ደስታ ልጅ ስትሆን አባቷ ደርግን በመቃወም ለረዥም ጊዜ በአገው ምድር ልዩ ስሙ ፋግታ የሚባል በታ በተደረገ ጦርነት ተሸንፎ ወደሱዳን ተሰደደ። ከዚያም ኢዲዩ የሚባል ፓርቲ በመቀላቀል ከደርግ ጋር ባደረጉት ጦርነት አብዛኛውን የጎንደር ክፍል ከያዙ በኋላ ወደባሕርዳር በመሄድ ለጦርነት ሲዘጋጁ በራሳቸው ወታደር እንደተገደሉ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚስተር ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ ጽፈዋል።
ልክ ነህ ወንድሜ ፡ ፋግታ የአያቴ አገር ነው ጀግና ያለበት አገር ነዉ ። እናቴም ለተወሰነ ጊዜ ከአባቷ ጋር ሸፍታ አባይን በክረምት በዋና ተሻግራ ከጠላት ጋር ስትዋደቅ ና ምንም ፍርሃት የማይሰማት ደፋር ና ጀግና ነበረች ነበር ።
የኔ እናት የኔ እናት አሳድጋን ነበር እና በተለይ በቋራ እሰክ መተከል ስላለሽልኝ በሂውት በጣም ነው ምወድሽ የኔ ጀገና
As a child I was there in Dangila town in Gojjam when her army invaded the town in 1976.
ይገርማል ትውልዷ ጎጃም ነው ዳንግላ ። ወንድሟ ቀኛዝማች ስሜነህ ልጅ ፍኖተሰላም አካባቢ አለ ። በስልክ እንደሚያገኛትም አጫውቶኛል ። ዙሮ ዙሮ የትም ትሁን ኢትዮጵያዊ ጀግና ነበረች ። ታሪኳ ተሰንዶ ቃለመጠየቅ ቢደረግላትና እውነቱን ከሷ ብንሰማ ።
ጎጃም አዘና አካባቢ እንደነበረችና ወያኔ 1983 ሲገባ ከቡሬ ሰባት ልጆች ሒደው ተቀላቅለው ተመልሰው መምጣታቸውን አስታውሳለሁ ።
I will tell you the truth. She is from Gonder Enqoyemesk kebele 11 arada.
አይ አማራ?በሕይወት ያለች ሴት ታሪክ እኮ ነው።
በጣም ትክክል
ምን ዋጋ አለው ስንቶች የሞቱለት ትግል እስከአሁን አላለቀም
ለኤልያስ ስለአያልነሽ ጥያቄ ካቀረቡት አንዱ ነበርኩ::በህይወት ስለመኖራ ሰማን::
ግን ቃለመጠይቅ ቢደረግላት በተለይ ስለ እነ ፀጋየ (ደብተራው) እድ ብዙ ታውቃለች ብዬ እገምታለሁ::
ኧረ ስለአያልነሽ ከዚህም በላይ ዘገባ ቢኖር መልካም ነው!እኔ ራሱ በልጅነቴ ገጠር ከብት እየጠበቅሁኝ እጅግ የበዛ ነገር ስእርሷ ሲወራ ትዝ ይለኛ በጣም ሚገርም ነው አለች በሕይወት?
በጣም ደስ ይላል ያየልነሽ የጦር ማሰልጠኛ እስካሁን ተከብሩ ይኖራል በአማራና በቤንሻጉል ደንበር
if she was fighter in 1960s how her age is 50?
አያልነሽ ስሜነህ በ78 አመተ ምህረት በጣና በለስ ፕርጄክት ሰራተኞች ላይ እገታ በማድረግ ሁለት፣ጣልያኖች በማገት ሱዳን ድንበር ላይ አድርሳ ሸኘቻቸዉ ያቃጠለቻቸዉ ማሽኖች ቢያናድደኝም የሴት ጀግና መሆኖ ያስደንቃል በወቅቱ የሳሊኒ ሰራተኛ ነበርኩ በወቅቱ የምትታገለዉ ለምን አንደሆነ ባይገባኝም
ጀግናዋ አያልነሽ ስሜነህ የአገዊቱ የነገስታት ዘር ነች
እዉነትም ጀግና እዉነትም ጀግና
ልጅ ሁፕ እምዎዶት❤❤❤❤❤❤❤❤
ያልተዘመረላት የዚያ ዘመን በፆታ የእናቶቻችን የእህቶቻችንና የልጆቻችን ተምሳሌት
የክፈለ ዘመኑ ፖሊቲከኛ
የዘመኑ የሴት ሽፍታ ነች።
ታላቅ ወንድሞ ነበራቸው አበባ ከበደ እስክንድር ከበደ የሽጥላ ከበደ በትክክል የአራዳ ልጆች ናቸው።
ሁሉም የእናቴ የአጎት ልጆች ናቸው አበባ ከበደ በህይወት አለች አበበ ከበደ ነብሱን ይማር አርፏል ለማንኛውም ታሪኳን እንዲ እንዲታወስ ስላደረጋቹ እናመሰግናለን
@@lunabetty4971 እስክንድርስ የት ነው?
@@marugeb6280 እስክንድር ያኔ ነዉ የሞተዉ
Simply i really really love this super legend. Hayalnesh is the name tattooed in my brain since i was a little boy..
አልም በማየቴ ድስ ብሎኛል
አያልነሸን በዜና በጣም ትልቅ ታርከ ያላት በጣም ታዋቄ ሰወነች አሁን ካሉት መሪዌች ያያልነሽን ታሪከ ለመነገር ይከብዳል እስከ አሁን ድረስ አያልነሽ አነዲ አሁንም ድረስ አንዲ ቋራ በርሀነች ነች አንዲ ባህርዳር ነች አንዲ ታስራለች በወያኔ ስርዓት ይባል ነበር አንዳ ጭልጋ :በመተከል ነው ያለች እየተባለ ይወራል ለምን ካለች በሄወት አታቀርቧትም በተም አሁነም ትልቅ ታጋይ ነች ❤
ሃምሳ ዓመት?
🙏🙏❤❤❤
❤❤❤
Is she alive? It is amazing.
እህቷ አለም ስሜነህ የናቴ ወዳጅ ነበረች እኛ ቤት ዉስጥ ትልቅ የፍቅር ቦታ ነበራት። እናቴ ልታገመኛት ትፈልጋለች
Oh my Hod , my childhood memory. I grew up up listening to about Aualnesh Simone. I used to scare when my family talk about her , they talk very silently with fear , like she was not visible, I didn’t think she was a living human , b/c I was a child
አያልነሽ የኔ አያል አያል የኔ አበባ
አበባ ለምለሚ ሳላይሽ መክርሜ...
አያልነሽ
Ayalenesh
ለፋኖ የትግል ልምድ ማካፈል አለባት!!!
በመጨረሻ አያልነሽ ታወሰች ጎንደር ያፈራቸው ብዙ ጀግኖች አስታዋሽ አላገኙም አውሮፖ ላይ ሁነው ይህን አድርጉ ሲሉን የነበሩት ብቻ ናቸው የሚተረክላቸው
ኧረ እባክሽ እውነት ከሆነ ለቃለ መጠይቅ አቅርቢያት
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉❤❤❤❤
አባቷም ደርግ አልገደለውም ። ታመውነው የሞቱት
I think her age is not less than 65 years old to the minimum.
ስሜ አድናቄሽነኝ እኔ ካአችጋራ አብረን ነበርን አዲሰላም አስታወሽ አልመራችን አይናለም ይባላአል አኔ ስሜአዲሡ ነወ የምባለው
ነበረች
ያልተጣራ ታሪክ ከማቅረብ ተቆጠቢ
ቅዘናም
በክት
Bahunu sehat 50 ametua new ? Jegininetua siwerra ene tiz yilegnal 80's layi
እጭ ትረካ ጠላሁ
አኔም ሰለ አያልነሸ ምንም ታለቃችን የትግል ጓድ በትሆንም ጀገንነት ግን በእርሷም በወንድሞቿ ነበር አያልነሸ የበርሃ ሰሟ በሆንም አበባ ከበደ ጀገንነት ከቤታቸው ነው የአንድ ሰፈር ልጆች ነን ግን በሒወት መኖሯን ስሰማ በጣም ደሰአለኝ በተጨማሪ የእኔ ጓደኞች አለምገዥ ከበደ የመክሊተ ልዮን የትእንዳሉ በውቅ ደሰይላል
በፖለቲካ አለም ወሰጥ የሴቶቾ ጀግንነትከጥንት ጀምሮ ያለ ቢሆነም በየትውም መሰከ ያሉትን ታሪካቸውን መመሰከር ያየነውን መሳወቅ ተገበ ነው በርቱ
ፋኖን መቀላቀል አለባት
ኢትዮጵያ አሁን የሚያስፈልጋት እንደ አያልነሽ የቆረጡ በኢህአፓ አይዲዮሎጂ የከተማ ትግል የሚያደርጉ ጀግኖች ናቸዉ
አያልነሽ 50 አመት ከሆነች እኔ እናቴ ሆድ ልግባ ይሆን? በጣም ያስጠላል እንዲህ ያለ ዉሸት ኧረዲያ!
😂😂❤ ye Ehapa tori ke 1970- 1983 meritalech bilalech Zegabiwa ke 1970 ke ahun 2016 46 amet honuwal keteweledech woyim tori memirat be sint ametuwa yihon yejemerechiwu ...... be gimit 20 amet bihon tori meri yehonechiwu 20+46 = 66 ametuwa yihonal be gimit
@@Praise24-7 ልክ አመጣሽዉ 66 አመት ይሆናታል ።16ቷን ከደበቁበት በርብረሽ ብቅ አረግሽዉ ፈጣሪ ላንቺ ይጨምርልሽ ።አሜን በይ
ጎጃም ከወያኔ ይልቅ አያልነሽ ስሟ የገነነ ነበር። ሕፃን ሆነን የደርግና የወያኔ ጭካኔ ሲነሣ አያልነሽ አለችልን እንል ነበር። አየልነሽ ምዕራብ ጎጃም ነው የተወለደችው ።ጎንደር አይደለም።
እኛ ቤተሰብ የአባቴ አክስት አያልነሽ የምትባል ነበረች ።ብዙ ጊዜ አያልነሽ እሷ ትመስለን ነበር።
እድሜ ላይ ውሸት ነው።
እከክ ነሽ
ልጅ እያለን መሳሪያ ሰራን የአያለሸ እንል ነበር
?...❤!!
ምን አያልነሸ ስሜነህ የሰሜነህ ልጅ አይደለችም አትበጥረቂ
አስታወስኳት:: እንደሚመስለኝ: ከ1985 ዓ.ም. ገደማ: አልታየችም:: የት: ገባች: ብዬ: አስብ: ነበር:: ደህና: መሆንዋን: በማወቄ: ደስ: ብሎኛል::
አያልነሽ፡የትውልድ፡ቦታዋና፡እድሜዋ፡አያወዛግብም፡በታሪክ፡ጀግንነቷይታወሰ።
ይች ባንዳ ምንድን ጥሩ ሰርታ ነው ያው ኢህፓ ጅዝባ ታጋይ ነው፡፡ የአማራ ጥላት ናት ይች የባንዳ ዘር ታሪኳን እንድጠፋ ነው ምናውቀው
መቆየት ደግ ነው አየን ብዙ መላ፣
እጅ ሳያቀብል በምላስ ሲበላ። የሚል ግጥም ያለበት የአያሌው መስፍን ዘፈን ትዝ አለኝ ። እንዲህ አዋውበሽ ስትተርኪያት ወደ ብፅእና ደረጃ ልታደርሻት ምንም አልቀረሽ። ጊዜው ሲረዝም ጊዜ እንዴት ነው የሕዝብ ወገን ሆና የተሳለችው?
አያልነሽ ከግብረ አበሮቿ ጋር ተራ የሽፍታና የወንበዴ ተግባር ስትፈፅም የነበረች ወንጀለኛ ነች። የዛሬ አርባ አመት 1976 መስከረም ወር መጨረሻ የማጠቢያ ወረዳ ዋና ከተማ የሆችውን ኩሊት ከተማን የሷ ሠራዊት (ኢህአፓ/ኢህአሠ) ተቆጣጠራት። ገና ጠዋት ነበረ ሰአቱ ። ያን ጊዜ 22 አመቴ ነው። በወቅቱ ያንን የጥፋት ቡድን ሲመሩ የነበሩት ጋይም (በ83 ወይም 84 አዲስ አበባ በኢህአዴግ የተገደለ) እና አሉላ የተባሉ ነበሩ ። ሁሉንም ሰው ሰበሰቡና የደርግን ፋሽሽትነት የእነርሱን ህዝባዊነት ከሰበኩ በኋላ :- " ይህች ከተማ ለደርግ ስትራቴጂካዊ ቦታ ስለሆነች ማለትም ከላይ እየተንደረደረ እየመጣ ማረፊያና እህል ውሃ እያገኘ እኛን ለማጥቃት ስለሚጠቀምባት እናቃጥላታለን፣ እናንተንም እዚህ እንዳናያችሁ ወደምትሄዱበት ጓዛችሁን ይዛችሁ ሂዱ ብለው ሠራዊታቸውን አሰማርተው ከተማዋን በመደዳ አቃጠሏት።ቤታችን ነደደ። በዚያን ጊዜ ያልተቃጠሉ የግለሰብ ቤቶች አራት ናቸው። እነሱም የተረፉት ቤተክርስቲያን አጠገብ ስለሆኑ እነዚያ ቤቶች ቢቃጠሉ ቤተክርስቲያኑ እንዳይቃጠል ተለምነው ነው። ሌላው ሳይቃጠል የቀረው ክሊኒኩ እና እንዲሁም ወደ ሽንፋ ገጥ ፈንጠር ብሎ ይገኝ የነበረው ESBU የሰራው ትምህርት ቤት ነው። በነገራችን ላይ ኩሊትን ኢዲዩም በ1969 እንዲሁ አቃጥሏት እንደገና ተሠርታ ነው።
መሄጃ ያለው በየመሄጃው ሲሄድ ስንት ህፃናት እና መጫቶች ከነደደው ቤታቸው ፊት ሆነው ሲያለቅሱ ማየት ልብ ይሰብር ነበር። ይሄ አልበቃ ብሎ ቢቸግረን ሽንፋ ከወንዙ ዳር ወርደን የሰፈርን በግምት ከመቶ ሃምሳ የማናንስ ሰዎች ከስድስት ወር በኋላ መጋቢት 2 ቀን እንደገና መጥተው ከዚህ አካባቢ ጥፉ አላልናችሁም ነበር ብለው በድጋሚ ዶጋ አመድ አድርገው ቤታችንን አቃጠሉብን። ያ ሁሉ ህዝብ ያለ መጠለያ በዚያ በረሃ ሆጭ ብሎ ሲታይ እጅግ ያሳዝናል። በዚያን ጊዜም አሉላ የተባለው የሠራዊቱ ኮማንደር ነው "እዚህ አካባቢ እንዳናያችሁ አላልናችሁም?" እያለ በቁጣ ሲያጉረጠርጥብን የነበረው። ከዚያ በኋላ ወደ ዳስ ፣ ሸኸዲ፣ ወደ መንዶካ፣ ሽኩርያ ፣ ዱራባ ፣ ቋራ ማዶ እንዲሁም ወደ ተለያየ ቦታ ሰዉ ተበታተነ።
እንዲህ ያለ የወንበዴ ድርጅት ኮማንደር ነች አያልነሽ። የሽፍታ ሥራ ሲሰራ የነበረው ድርጅት በአንድ ወቅት እንፈልግሃለን ብሎም አያልነሽ ባለችበት ሰርፈረዲ ድረስ ተወስጄም "መጋቢት 2 ቀን ቤትህ ሲቃጠል ተቆጥተሃል ተብዬ 400 ብር ከፍዬ ነው ከአንድ ቀን በኋላ የተመለስኩት። ከእኛ ጋር ለምን አትታገልም ብለውም ይጠይቃሉ አያፍሩም።ሌቦች። እንዲህ ያለው አሸባሪ አላጢስ እና ገለጉ ተደብቆ በኃይለሥላሴ ጊዜ ሳይቀር ዝሆን እና አነበሳ ገድለሃል እያለ ገበሬን በቅጣት ቁም ስቅሉን ሲያሳይ የነበረ ድርጅት ኮማንደርን ጀግና ስትያት መስማት በጣም የሚያሳምም ነው። ሚዛን ይኑራችሁ። የተጎዱ ንጹሃን ዜጎችም ይኖራሉ ማለትን ተማሩ። በፍርሃት አገር የሚያቃጥል ፣ የድሃን ቤት እያቃጠለ ለፀሐይና ለቁር የሚዳርግ የሽፍቶች ስብስብ ነው እኛ የምናውቀው ኢህአፓ። እሷም አንዲት ተራ ሽፍታና የሽፍታ አለቃ ነበረች።
ጅብ እማያውቁት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ እንደሚባለው ነው። ድሃን ማሸበር ነበር ስራዋ ፣ሌላ የለም።
Jegena 🎉🎉🎉
Ahun ye 50 Amet Edme Kalat Ena 1969 Torinet Wust Keneberech Tigil Yejemerechiw Enatwa Mahesen Wust Eyalech Mehon Alebet
EDAMWANEM LKHE AYDALEME GEN ANCH ALWAKSHEM. BANCH AFFE SAYHOUNE ABERAWATE YANBERU YANAGERU.DERG EKO 50 AMTE HUONAW.ATZABERKI.KADQDA
እና አሁን ፉኖን ተቀላቀለ አለው እዚሁ አጠገባችን ናት ብዙ አትበጥረቂ
እባካችሁ የዝችን ጀግና የነጻነት ታጋይ ታሪክ ጽፋችሁ ለታሪክ ብታስቀምጡና ትዉልዱ ቢማርበት እላለሁ።
አያልነሽ ክፍል ሁለት th-cam.com/video/vkGwobQOjkQ/w-d-xo.htmlsi=lUewEcH7U-GYf0Cp
Yachefer sew endehonech new yeminawekew tariku yitara
አያቴ ከሰሜነሕ ደስታ ጋር አብረዉ ሸፍተዉ ነበር ይገርማል አበሳ ያበሳ ልጅ
የአያልነሺ ጦር ከባህዳር ወጣ ብሎ የአራተኛ ሜካነይዝድ አባል የነበረ ጉደኛዬን ጎንደር ሀሙሲት ላይ ገላዋለች በ1981 ቃኝ ነበር
ብዙ ታሪክ አዘብሽ አስተካክዬ ብዙ ስህተት አለበት ንግግርሽ
50🙉
ስሟ አያልነሽ ስሜነህ አይደለም። ስሟ ዓለም ገዥ ከበደ ነው። ተስተካክሎ ይነገር።
ማሰተካከያ ሰሟ አበባ ከበደ ነው ታናሸ እህቷ አለምገዥ ከበደ ነው
ወያኔ ከሚያወድሳቸዉ እና ለማን እና ለምን እንደታገሉ ከማይታወቀዉ ሴት ታጋይ ከሚላቸዉ ከንቱዎች ይልቅ የዚህች ጀግና ታሪክ ሪከርዱን የሰቀለ/ተወዳዳሪ የማይገኝለት ነዉ፤፤
Hiiy አያአልነሽ ሰሚነሰላምነሽ ወይ
አለምገዝ እያት
ታሪክ አታዛቡ እባካችሁ!!!
እኔ ግን ጎጃም እንደሆነች ነው የማቀው
HiiAyalnsh seMenH
እስከ 27 ኢትዮጵያ ኖራለች ያልሺው ስህተት ነው። ቢያንስ ከመላሳ አመት በላይ ይሆናታል። ዕድሜዋም አምሳ ብቻ አይደለም። ኢህአፓ ራሱ ሀምሳ አመት አለፈው።
እበክህ ጦረኛ መቼ አጠን አሁንስ ሞልተውልን የለም
አያልነሽ የቀኝ አዝማች ስሜነህ ደስታ ልጅ ከሆነች ታናሽ እህትና ወንድሞች ነበርዋት እነሱም ደስታ ስሜነህ : ዮሴፍ ስሜነህ : አየሁ አለም ስሜነህ ናቸው እንጅባራ ነበር የሚኖሩት እድሜዋም 60 - 65 ይሆናል
Enatuan akachewalehu surba bifeta ketebale bota bebihtwan nurew alfewal. Sekela new hegerua. Abatiwa kegn azimach simeneh yibalal. Be tinbit neber yeteweledechiw. Yekerebew tarik sihtet new.
ከይቅርታ ጋር ከ1970 እሰከ 1973 የኢሐአሰ መሪ የነበረችዉን ጀግኒት እድሜዋን አሳስታችሑታል. የጀግና ታሪክ ምንም ጭማሪ አያስፈልገዉም. ታሪክዋን አትበርዙት.
እኔ ስለማውቃት አያልነሽ ነው ያወራሺው ወይስ ሌላ አያልነሽ??? በይ የሚያውቋትን ወንድሞች ፈልገሽ አግኛቸውና ትክክለኛ ታሪኳን አቅርቢ! እድሉን ካገኘሽ ፋኖ አርበኛ መሳፍንት በቅርብ የሚያውቃትና አብሯትም የታገለ ታላቅ ወንድም አለው፣ አፈላልገሽ አግኚውና ሙሉ ታሪኳን ይነግርሻል። ያሬድ ጥበቡንም ከገኘሺው ይረዳሻል። በተረፈ ይህንን ቪዲዮ አውርጂው።
Wrong narration She is born and grown up in Gojjam
ኮረኔል አያልነሽ
ዜናው ትክክል ነው ግን አያልነሸ ሥሜነህ ደስታ ትወልዷ በታሪክ እንደሠማሀት
ጓጃም ዳንግላ ኳኩራ ናት
Wrong history # she is from Gojjam
For me the same gojjm gonder yaw new
ዐየዕድሜ ጉዳይ አስተካክሉት ; ዛሬ 50ዓመት ከሞላት እስክንድር ከበደ የመጣ ጊዜ ከጎና የነበረው ልጀ የተዋወቃት 1969ከሆነ በእናንተ የዕድሜ ስሌት ልክ አይደለም:: 1978 ለስራ ጉዳይ ፖዊ ሄጄ ነበረ ስለአያልነሽ ዳንግላ መግባት ስለ ሰማሁ ወደ ቁንዝል የዘር ማባዣ በፍቃደኝነት አያልነሽን ለመቀላቀል መሄድ ጠይኩ ተፈቀደልኝ በሄድኩ በነ ተው ቁንዝል ኢንፎርሚሽን መሰብሰብ ጀመርኩ አንዱ ወደ ዳንግላ ሲሄድ መንገድ ላይ እንዳስቆማቸው ነገረኝ : በአረቄ ቤት ማታ ላይ አውቄ ስለ አያልነሽ በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ ለማግኘት ስል " እረ አያልነሽ ሳትመጣብኝ በጊዜ ወደ ቤት ልግባ ስል በሙሉ ጠጪዎች ማለት ይቻላል " አንተን አትነካህም እሱ የምትፈልገው ኢሰፓ አባል ነው ነበር የሚለኝ" በዛ በዛ ስል በአንድ ወር ጊዜ ውሰጥ ሳትመጣ ቀረች እኔም ባላስብኩበት ወቅት የድርጀት መኪና መጥቶ ተነስ በቃ እንሄድ አሉኝ
አያልነሽን በ1983 ዓ'ም በአይኔ ያየኋት መቐለ ከተማ ላይ በምርኮ እያለች ነውና አድናቂዎቿ ነበርን አንድ ነገር ላስታውሳት እስቲ ምናልባት ካስታወሰች ያኔ የአያልነሽ ጦር ለብሰውት የነበረው አንሶላ አቦጀዲድ ሆኖ በእንኮይ ቅርፊት ነው መሰለኝ ይቀቅሉትና አንሶላው ቀይ ከለር ነበረው ክክክክ
ምንዋጋ አለው ጀግና እግዚአብሔር ብቻ ነው ;; ታግላችሁ ምን አመጣችሁ ጭራሽ ለዓረብ የተሽጠች አገር አረጋችኇት ::
ስሜነህ የጎጃም ሽፍታ አልነበረም እንዴ???
በህይወት አለች? የሚገርም ነው!!!! ደርግንና ወያኔን ውሃ ውሃ ያሰኘች ምርጥ ኢሕአፓ ነበረቸ። እድሜዋ ግን ይስተካከል። ከ60 እስከ 63 ይሆናታል። ያውም በጣም በልጅነት ኢሕአፓን ሰለተቀላቀለች።
አንቺን ሳስብ እቀናለሁ። ደግሞ እንደምንፈልገው ስላላገኘንሽ ይቆጨኛል። እመብርሃንን እወድሻለሁ....
አንቺን ሳስብ እቀናለሁ። ደግሞ እንደምንፈልገው ስላላገኘንሽ ይቆጨኛል። እመብርሃንን እወድሻለሁ
Lemagn tigre .. yihew 1 million 200 shi tigre asgedelech lela min ametach. 😅😅 shermuta lemagn tigre
why lie?
መግቢያው የሪልስቴት ማስታወቂያ መስሎኝ 😀በልጅነታችን አዋቂዎች ከስንት አንዴ ሲያወሩ በዝና እንጂ በፎቶ የማላውቃትን አያልነሽ ስላየሗት ደስ ብሎኛል። የአተራረክ መዛነፉ ቢስተካከል። 'አያልነሽ በልጅነቷ ደርግም ኢህአዴግም ለህዝብ የማይጠቅሙ ትልነበር' ብላ ተራኪዋ ስት ተርክ ቲነሽ ግር ይላል። ለምን አያልነሽ የምትታወወቀው በደርግ ጊዜ ነው ማለትም በሰባና ሰማኒያዎቹ፣ ያኔ ደግሞ ደርግና ተቀናቃኞቹ ኢህአፓና ከአማጺዎቹ ሻቢያና ወያኔ እንጂ ኢህአዴግ የሚባል ነገር የለም። ኢህአዲግ ከ1983 በሁዋላ ወያኔ ጠፍጥፎ የሰራዉና በዋነኝነት የሚዘውረው የፓርቲዎች ስብስብ ነው። ለላው እድሜዋ ባሁኑ ሰአት 50 ነው የተባለዉም አያሳምንም፣ ለምን ቢባል በ1970 ና 80ዎቹ ጉልህ ሚና የነበረ ሰው በቲኒሹ 20 አመት ቢሆነው ዛሬ ላይ 65 አመት አዛውንት ስለሚሆን ነው።
ሐያልነሽ፣ አቤቤቤቤት ጭካኔሽ፣ በዛ እድሜሽ ጭቆናን ተጠይፈሽ ጫካ የገባሽ ጀግና አሁን ምን ነክቶሽ አገር እንዲህ ሲበጠበጥ ዝምምም ማለትሽ?? እኔ የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ ነኝ ግን ስላንቺ ጀግንነት ስሰማ ነው ያደኩት፣ አቤቤቤት ጭካኔሽ እስከዛሬ ስለአገርሽ ፀጥ ማለትሽ
ሰው ለምን የማየውቀውን ነገር እንደ ሚዘበዝብ ሁሌ ግራ ይገበኛል።
አያልነሽ የጎንደር ሰው አይደለችም። ቀኘ/ ሰመነህ ደስታ የጎንደር ሰው አይደለም። እርግጥ አያልነሽ ኢሕአፓ ነበረች።
አያልነሽን ጥበብ ጠራት ? አያልነሽ በ1970 በጓድ ንጉሤ ተፈራ ተምዘግዛጊ ጥይት ቀለበት ውስጥ ተቆልፋለች:: እና ጓዶች ምንም እንኳ ታሪክ የሚዎራለት ሠው ቢጠፋም የሞቱትን አሉ እያላችሁ አዲስ ታሪክ አትፍጠሩ::