የህጻን ሶሊያና ዳንኤል ሰራቂ ፅኑ እስራት ተፈረደባት!ሶሊያና ሰው መቅረብ ተቸግራ ነበር(
ฝัง
- เผยแพร่เมื่อ 5 ก.ย. 2024
- ሶሊያና ዳንኤል#የህጻን ሶሊያና ዳንኤል ሰራቂ ፍርድ
የ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣች
ሶሊያና ዳንኤል የተባለችውን የሁለት ዓመት ሕፃን በመጥለፍ እና በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣች፡፡
ሕፃን ሶሊያና ዳንኤል በቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ የተወሰደችው መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ሳሪስ አዲስ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነበር፡፡
ቤዛዊት በቀለ በተባለችው የቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ የተወሰደችውን ሕፃን ለማግኘት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሐየራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት፣ ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች እና አካባቢዎች በመሄድ ጭምር አስፈላጊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ከፍተኛ ጥረትን የጠየቀ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ፖሊስ አስታውሷል፡፡
በተደረገው ክትትልም ቤዛዊት በቀለ መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ሱሉልታ ከተማ "ኖኖ መና አቢቹ" ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሕፃን ሶሊያና ዳንኤልን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በቁጥጥር ስር መዋሏ ይታወሳል፡፡
እንደ አዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ፤ ግለሰቧ በቁጥጥር ስር መዋሏን ተከትሎ ፖሊስ ባከናወነው ምርመራ የማስፋት ስራ ከዚህ ቀደም በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችባቸው 5 የተለያዩ ቤቶች ውስጥ ልዩ ልዩ ንብረቶችን መስረቋ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡
ከሰረቀቻቸው ንብረቶች መካከልም 2 ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 1 ሞባይል ስልክ እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎች ፖሊስ ባደረገው ጥረት ከሸጠችበት በምሪት እንዲመለሱ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡
በግለሰቧ ላይ ምርመራ ተጣርቶ በከባድ ስርቆት እና ሕፃን ልጅ መጥለፍ በሚል ወንጀል በአቃቤ ሕግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ቤዛዊት በቀለ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
0937938528 0951090999 ATO Daneil the father
እኳንም ታሠረች አልሀምዱልላ አላህ ዟሊሞችን ያዋረዳቸው
እንኳን ደስ አላችሁ
በጣም ጥሩ ነው ለሌላም መቀጣጫ ይሆናል ኤላ እናመሰግናለን።
እድለኝ ናቸው ❤❤🎉🎉
ሶልያና ዳኒ እድግ በይ
እንኮን በሰላም መጣህ ኤልያስ እርጋታህንና ስን ስረአትህን ስወድልህ የመዳም ቅመሞች እረ በአላህ እናሳድገዉ ወድማችንን
❤❤❤❤❤🎉🎉🎉
እንክዋን ደስ አለህ
ህጉ እኩል ቢሆን ጥሩነበር
ሑለት ሕጻናት እሕትማማቾቹን ያረደችዉስ????????????
ጎሽ ፍርዱንም እንዲህ አሰሙን!!
1ኛ ነኝ
ቅጣት. ነው.
👍👍👍🥰🥰🥰🥰
አአ ውስጥ ስንት አሉ ንሱ ህዝቦች እየሰረፉ እና እየገደሉ በነፃ የሚለቀ ቁ። ግን ደሀ እደሰራተኛዋ አይነት 18 አመት በእስርቤት ይበሰብሳል። in Ethiopia there is no human right. If you have no money, you are nothing in Ethiopia. That it
በአሁኑ ሰአት ሰራተኛ ስንቀጥር ፎቶ እናንሳቸው በቅርብ የሰማነው አንድ ሰራተኛ ከአንድ ቤት ሶስት laptop ሰርቃለች
የዘቢባ ባል ነው እንዴ ሰውየው
🤣🤣🤣ymesaséalu ngegru lerasu ygermal
ቆይ ግን ያሰሪዎችንስ ክፋት ማን ይናገር
እና እነሱ ክፉ ቢሆኑ ልጅቱ መሰሩቅ ነበረባት???
ይህ ያልወለደ ሰው ኮሜንት ነው😡
@@asnakutigabu4301 ትክክል ናት አላልኩም ።
Yehe Ygered Coment nw
ይህ ኮሜንት ያልወለደ ሰው ነው 😢🇪🇷
@@user-px6sj7ul8w(ከይቅርታ ጋራ ) እንዳንድ ግዜ ለሌሎች በምንሰጠው አሰተያየት የብዙዎችን ሞራል ሰለምንነካ የአማርኛ ዘይባዊ /ፈሊጣዊ አነጋገር አክለን ብንፅፍ ጥሩ ነው(👉 ሁሉም ያልወለዱ ሁሉ ጨካኞች ናቸው አያሰብልም 3ት ወልደው የሰው ልጅን ቀጥቅጦ የገደለሰ እንዳለ ይታወቃል 👉ይህሰ በምን ትርጉም ታይቶ ነው ።