ไม่สามารถเล่นวิดีโอนี้
ขออภัยในความไม่สะดวก

ለፓርላማ የተመራው የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የሚፈቅደው የአዋጅ ማሻሻያ ምን ይዟል?

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 14 มิ.ย. 2024
  • የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እንዲገቡ የሚፈቅደው የባንክ ስራ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ። የአዋጅ ማሻሻያው፤ የባንክ አገልግሎት ዘርፍን “ለመምራት፣ የፈቃድ አሰጣጥን ለመወሰን እና ለማስተዳደር” የሚያስችል ሆኖ እንደተዘጋጀ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
    የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 7፤ 2016 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የባንክ ስራ አዋጅ ማሻሻያን ጨምሮ አምስት የአዋጅ ረቂቆች ለፓርላማ እንዲቀርቡ ውሳኔ አሳልፏል። የባንክ ስራን መፍቀድ እና መቆጣጠርን የተመለከተ አዋጅ በመጀመሪያ የወጣው በ1986 ዓ.ም ነበር። ይህ አዋጅ በ2000 ዓ.ም በጸደቀ “የባንክ ስራ አዋጅ” ተተክቷል።
    አሁን በስራ ላይ ያለው “የባንክ ስራ አዋጅ”፤ የተወሰኑ ማሻሻያዎችን አካትቶ ከአራት ዓመት በፊት በፓርላማ የጸደቀ ነው። ይህ አዋጅ በድጋሚ እንዲሻሻል የተደረገው፤ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት የባንክ ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስተሮች የሚከፍት ፖሊሲ ተግባራዊ እንዲሆን በነሐሴ 2014 ዓ.ም መወሰኑን ተከትሎ ነው። (ኢትዮጲያ ኢንሳይደር)
    ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
    -------------------------------------------------------------------------------------------
    ኢትዮጲያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
    ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
    ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
    ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
    ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
    ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

ความคิดเห็น •