ไม่สามารถเล่นวิดีโอนี้
ขออภัยในความไม่สะดวก

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በስድስት ዓመት ለአራተኛ ጊዜ አዲስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተሾመለት

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 30 มิ.ย. 2024
  • የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት፣ አስተዳደር እና አመራርን በበላይነት የመምራት ኃላፊነት ለተጣለበት ኮርፖሬሽን፤ በስድስት ዓመት ውስጥ ለአራተኛ ጊዜ አዲስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተሾመለት። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽንን እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙት፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍስሃ ይታገሱ ናቸው።
    ከመንግስት ግዙፍ የልማት ድርጅቶች አንዱ የሆነው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተመሰረተው በ2006 ዓ.ም ነው። ተቋሙ አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ 12 የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በስሩ ያስተዳድራል። በድሬዳዋ የሚገኘው ነጻ የንግድ ቀጠናም በኮርፖሬሽኑ ስር ያለ ነው።
    ተቋሙን ላለፈው አንድ ዓመት ከስምንት ወራት በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩት አቶ አክሊሉ ታደሰ እና አዲሱ ተሿሚ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 24፤ 2016 የስራ ርክክብ ማድረጋቸውን ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል። ዶ/ር ፍስሃ ወደ አሁኑ የኃላፊነት ቦታ ከመምጣታቸው አስቀድሞ ላለፉት ስድስት ወራት በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰርተዋል። (ኢትዮጲያ ኢንሳይደር)
    ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
    -------------------------------------------------------------------------------------------
    የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
    ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
    ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
    ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
    ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
    ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

ความคิดเห็น • 1