የአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ቅበላ ፖሊሲን በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡|with amih |

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 17 ก.ย. 2024
  • አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተማሪዎች ቅበላ አሰራርን ከ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
    አሰራሩ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ እና ልዩ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ማስተማሪያ ተቋም ያደርገዋል፡፡
    ይህን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።
    ***
    ከ2017 ዓ.ም የትመህርት ዘመን ጀምሮ ስለሚተገበረው የተማሪዎች ቅበላ አሰራር ዋና ዋና ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው፣
    👉 አዲሱ የተማሪዎች ቅበላ አሰራር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት በሚያደርገው የሽግግር ሂደት አንድ አካል ነው
    👉 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ እና ልዩ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ማስተማሪያ ተቋም ያደርገዋል
    👉 አሰራሩ የሚተገበረው በመጪው የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው አዲስ የቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ጀምሮ ነው
    👉 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች የተዘጋጀውን የመወዳደሪያ ነጥብ ፣ የመግቢያ ፈተና እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶችን ሲያሟሉ ብቻ ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚገቡ ይሆናል
    👉 የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ፍትሐዊ የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት ፣ ኢትዮጵያ በመጪው ዘመን የምትፈልገውን ብቁ ምሩቃንን ለማፍራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማዘጋጀት የሚያስችል ነው
    👉 አሰራሩ በመንግስት ወጪ የሚሸፈን የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) እና በግል ወጪን በመሸፈን የተማሪዎችን ስብጥር በጠበቀ መልኩ ማስተናገድ እንዲያስችል ተደርጎ የተቀረጸ ነው
    👉 አዲሱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ቅበላ ስርዓት ለቅድመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች በፖሊሲው እና በመመሪያው መሰረት የሚተገበር ሆኖ፣
    1. ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና ከታዳጊ ክልል ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት ፍትሓዊነቱ ይረጋገጣል፡፡
    2. መንግስት ከፍተኛ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለሀገር በሚፈለጉ የስልጠና መስኮች ወጪን ጭምር በመሸፈን የሚያስተናግድበት ስርዓት ይኖራል፡፡
    3. በገበያው እጅግ ተፈላጊ በሆኑ የትምህርት መስኮች ጥራት፣ ፍትሐዊነት እና ብዝሀነት ሳይዘነጋ በራሳቸው የትምህርት እና ሌሎች ወጪያቸውን ሸፍነው ለሚማሩ ተማሪዎች እድል ተመቻችቷል፡፡
    በ2014፣ 2015 እና 2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች የሚወጣውን መስፈርት ታሳቢ አድርገው በዩኒቨርሲቲው ፖርታል portal.aau.edu.et መመዝገብ ይችላሉ።
    @addisababauniversityofficial

ความคิดเห็น • 6

  • @withamih
    @withamih  14 วันที่ผ่านมา +3

    comment your question, if anything makes you confused, under here.
    Don't forget to turn on the caption. I included some information in it!
    if you need more clearance you can watch this video: th-cam.com/video/0guoVn0Xwxc/w-d-xo.htmlsi=sIu96jVS7ig_zars
    Also join this telegram group to share information: t.me/AAU_SSS_and_GSS
    Here is a channel: t.me/AAU_SS_and_GS

  • @KebedeKuma
    @KebedeKuma 2 วันที่ผ่านมา

    Why Examination ceneters given in addis ababa only????

  • @bezualemzegaye9510
    @bezualemzegaye9510 3 วันที่ผ่านมา

    Be distance lememezgeb be evening bemilew new mikatetew

  • @withamih
    @withamih  14 วันที่ผ่านมา +1

    You can register here: portal.aau.edu.et/

  • @GAMEESPECIALIST
    @GAMEESPECIALIST 14 ชั่วโมงที่ผ่านมา +1

    1. UAT tefetenen, fetenawen kalefen, self-sponsor hunen yefelegenewen field memar enchelalen.
    2. UAT benewek, self-sponsor hunen megebat anchelem.kefelegenw field gar
    3. UAT alefen, self-sponsor kehonen, minimum be'amet sent enkefelalen.
    .

    • @withamih
      @withamih  14 ชั่วโมงที่ผ่านมา

      1. Not only passing you are expected to score high marks to get the department you would like to join.
      2. If you fail, yes they uv do not accept you.
      3. t.me/AAU_SS_and_GS join this channel