ገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥም ሲያነብ፦ “በባዕድ አገር” “ፍቅርሽን በፍቅሬ በፍቅርሽ ልቅመሰው”

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 10 ก.ย. 2024

ความคิดเห็น • 2

  • @birukfekadu
    @birukfekadu 3 ปีที่แล้ว +5

    እኔ እወድሻለሁ
    /ገብረክርስቶስ ደስታ /
    ብዙ ሺህ ዘመናት
    እልፍ አእላፍ ሌሊት
    ሚሊዮን መሰለኝ
    ፍቅሬ አንችን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ።
    እኔ እወድሻለሁ
    የሰማይ መሬቱን
    የባህር ስፋቱን
    የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
    እንደ ፅጌ-ረዳ
    እንደ አደይ አበባ
    እንደ ሎሚ ሽታ፡፡
    እንደ እጣን ጢስ እንጨት፣ እንደ ከርቤ ብርጉድ፣
    እኔ እወድሻለሁ፣
    አበባ እንዳየ ንብ፡፡
    እንደ ቢራቢሮ ጫካ እንደሚያስሰው
    ፍቅርሽን በፍቅሬ በፍቅርሽ ልቅመሰው
    ማር ወለላዬ ነሽ ከረሜላ ስኩዋር
    አማርኛ አይበቃ፤
    ወይ ጉድ!
    ባለም ቋንቋ ሁሉ ቢወራ ቢነገር፣
    እኔ እወድሻለሁ
    እንደማታ ጀንበር።
    እንደ ጨረቃ ጌጥ፣ እንደ ንጋት ኮከብ፣
    እኔ እማልጠግብሽ
    ስወድሽ፣ ስወድሽ፣ ስወድሽ፣ ስወድሽ፡፡
    ጡት እንዳየ ህፃን ወተት እንዳማረው
    ጠጋ በይ ዘመዴ አፍሽ ህይወቴ ነው።
    ጣይ እንዳየ ቅቤ
    ገላዬ ገላሽን ሲነካ የሚያልቀው፣
    አፈር መሬት ትቢያ ውሃ እንደሚበላው፣
    ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ
    ብዙ ሺህ ዘመናት
    እልፍ አእላፍ ሌሊት
    ውድ እወድሻለሁ፣
    ዐይኖችሽን ባይኔ ተዳክሜ እያየሁ
    ስወድሽ ስወድሽ
    እኔ እወድሻለሁ።
    16/9/1960ዓ.ም የኢትዮጵያ ድምጽ ጋዜጣ
    /ገብረክርስቶስ ደስታ/

  • @hamh3998
    @hamh3998 3 ปีที่แล้ว +1

    ለመጀመርያ ግዜ የሰማውትም ሸገር ላይ ነው። በሰማውት በወሩ በዘፈን ተለቀቀ። የትልቅ ሰው ስራ በትልልቆቹ ሲቀርብ ይረዱታል። ጋሽ ገ/ክርስቶስ ደታ። ውዴ ስወድሽ!!