Tesfaye Gabiso Selected Songs👍እግዚአብሔር ሲረዳ 👏ነፍሴ ወደ አምላኳ 👏🏼በእውነት አሳድገን👏🏼ለምን ወደድከኝ አልልህም👍

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 14 ต.ค. 2024
  • 1. እግዚአብሔር ሲረዳ
    በህይወት ጎዳና ፈተና ቢበዛም
    ጌታን እየጠራ ንጹህ ሰው አይጠፋም
    እጄን ያዘኝ ብሎ ሲጮህ ይሰማዋል
    ከረግረግ አውጥቶ በድል ይመራዋል
    እግዚአብሄር ሲረዳ ከሰማያት ወርዶ
    በደልን ሲያስወግድ በቅንነት ፈርዶ
    አላያችሁም ወይ ወጥመዱ ሲሰበር
    ምርኮኛው ተለቆ ማዳኑን ሲናገር
    ችግረኛውን ሊውጥ ጠላት ስንደረደር
    በሚያስፈራራ ቃል በትዕቢት ሲናገር
    ደርሶ የሚታደግ እግዚአብሄር ብቻ ነው
    በሰው መታመን ግን የከንቱ ከንቱ ነው
    ያለውን ተነጥቆ ሁሉን ነገር አጥቶ
    በአጠገቡ የሚቆም ጌታ ብቻ ቀርቶ
    በእንግድነት አገር ተገርፎ ለሚያልፈው
    ተስፋው መሰረቱ አምላኩ ብቻ ነው
    የቅዱሳን ረድዔት ከሰማይ ይመጣል
    ዘመናትን ቆጥሮ ጌታ ይመለሳል
    የልጆቹን እንባ ከአይናቸው ያብሳል
    ክብርና ምስጋና ለስሙ ይሆናል
    2. ነፍሴ ወደ አምላኳ ስጋም ወደ አገሩ
    ነፍሴ ወደ አምላኳ ስጋም ወደ አገሩ ሳይመለስ
    ቶሎ ቶሎ ብየ ስራየን ልጨርስ
    ነፍሴ ወደ አምላኳ ስጋም ወደ አገሩ ሳይመለስ
    ሌት ከቀን ልስራና ስራዬን ልጨርስ
    ሲተጉ የሚያገኛቸው ሲመጣ ጌታቸው
    ከመክሊታቸው የቀሩ ምስጋና አላቸው
    አገልግሎቱን ያልናቀ በጥቂቱ ታምኖ
    ብድራቱን ይቀበላል ስራው ተፈትኖ
    አደራው ከቶ የማይገዳቸው ቸልተኞች
    የጌታቸውን መመለስ የረሱ ዝንጉዎች
    ብድራቸው ለቅሶ ነውና ዋይታ እንዳይጠብቀኝ
    መንፈስህ ዘወትር ያንቃኝ ለክብርህ አቁመኝ
    ጥቂት ታይቶ በኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት
    እንደሆነ መቸ አጣሁት ከቶ የኔ ህይወት
    እንግዲያውስ ታከተኝ ሳልል ልሩጥ ለጌታዬ
    የሰነፍ ሰው ሞት እንዳልሞት ልትጋ በአላማዬ
    መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ አበቃሁኝ
    ሀይማኖቴን ጠብቂያለሁ ሩጫውን ጨረስኩኝ
    እንደ ጳውሎስ ለማለት ተፈጸመ እንደ እየሱስ
    ምስጋናዬንም እንዳቀርብ ለሰራዊት ንጉስ
    3. በእውነት አሳድገን
    በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር
    በከንቱ መታበያችን ይቅር
    በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር
    በክርስትናችን እድሜ ቆጥረን
    በልምዳችን ቆርጠን
    በትህትና መማሩ ቀረና
    እድገታችን ቆመ ታበይንና
    በአስተያታችን ጠቢባን ነን
    ትንኝን እናጠራለን
    ራሳችንን ማንጻት ሳይቻለን
    የሌላውን ጉድፍ እናያለን
    ማለዳችንን እዩልን እያልን
    በከንቱም እየታበይን
    አንትንም በዚህ እያሳዘንን
    ሳይታወቀን ስንቶችን ጎዳን
    እንደህጻናት ጨዋዎች አድርገን
    ንጹሁን ልብ መልስልን
    አይናችንንም እየገለጥን
    አንተው አመላልሰን በብርሃንህ
    በቃልህ ስርአት ቦታ ሁነን
    በፍቅር እየታነጽን
    በእውነት እንደግ ወደ እየሱስ
    እየታበይን ለምን እንነስ
    4. ለምን ወደድከኝ አልልህም
    ለምን ወደድከኝ አልልህም በርግጥ ወደኸኛል
    የፍቅርህ መግለጫ ይሄ ነው ለኔ ተወግተሃል
    አንት ለኔ የሆንከውን ያህል እኔ ላንተ አልሆንኩም
    ምን ያህል እንደሆነ አላውቅም ለክቸ አላየሁም
    ግን አንድ ነገር አውቃለሁ ስለወደድከኝ እወድሃለሁ(2)
    ከርግማን ስለዋጀኸኝ ሞተህ ሸክሜን ስለወሰድክ
    በመንፈስ ቅዱስ ስለሞላኸኝ ነፍሴን ስለባረክ
    ጸጋን አብዝተህ ስለሰጠኸኝ ከቶም ስላልተውከኝ
    ምን ያህል እንደሆነ አላውቅም ለክቸ አላየሁም
    ግን አንድ ነገር አውቃለሁ ስለወደድከኝ እወድሃለሁ (2)
    ደስ ላሰኝህ እጥራለሁ በህይወቴ ላከብርህ
    ሆኖም ከቶ አልጠቀምኩህም ሁሌ ሳሳዝንህ
    ይልቅ ብዙ አድክሜሃለሁ የትም እየቀረሁኝ
    ብዙም ስላላፈራሁ እየሱስ ከፍቶኝ አለቅሳለሁኝ
    ግን አንድ ነገር አውቃለሁ ስለወደድከኝ እወድሃለሁ (2)

ความคิดเห็น • 21