ไม่สามารถเล่นวิดีโอนี้
ขออภัยในความไม่สะดวก

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ ቢያንስ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 17 มิ.ย. 2024
  • በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ጅጋ ከተማ፤ ቢያንስ 18 ሰዎች “በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን” አራት የከተማው ነዋሪዎች “ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ብሔራዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ “በአካባቢው ጥቃት ተፈጽሟል” የሚል መረጃ እንደደረሰው ገልጾ፤ ክስተቱን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል።
    የዓይን እማኞቹ፤ የጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የተገደሉበት ክስተት የተፈጸመው ከትላንት በስቲያ እሁድ ሰኔ 9፤ 2016 አመሻሽ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ ዕለት 11 ሰዓት ተኩል ገደማ፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑ “ሶስት ፓትሮል” ተሽከርካሪዎች ከደንበጫ ወደ ጅጋ ከተማ እየገቡ በነበረበት ወቅት፤ “በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት” ከፊት በነበረው መኪና ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ መሸሻቸውን የዓይን እማኞቹ አብራርተዋል።
    ጥቃት ከደረሰበት መኪና ኋላ የነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፤ በጥቃቱ “የወደቁትን አባሎቻቸውን” እነርሱ በነበሩባቸው ተሽከርካሪዎች ላይ ጭነው መሄዳቸውንም የከተማይቱ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከደቂቃዎች በኋላ “የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች” ወደ መሃል ከተማ በመምጣት፤ በዚያ የነበሩ ሰዎችን ጥይት በመተኮስ መግደላቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በስልክ ያነጋገረቻቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች አስረድተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
    ተጨማሪውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ ethiopiainside...
    -------------------------------------------------------------------------------------------
    የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
    ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
    ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
    ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
    ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
    ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

ความคิดเห็น •