ไม่สามารถเล่นวิดีโอนี้
ขออภัยในความไม่สะดวก

ዜና| ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ከኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነርነታቸው በመጪው ሐምሌ ወር ሊሰናበቱ ነው | Ethiopia | Daniel Bekele | Human Rights

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 18 ส.ค. 2024
  • የሰብአዊ መብት ተቋማት ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ወይም አጋር ሀገራት ገንዘብ ማሰባሰባቸው፤ “ነጻነታቸውን የሚቃረን” ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተናገሩ። እርሳቸው የሚመሩት ተቋም ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ገንዘብ ቢያሰባስብም፤ “ማናቸውም አይነት ተጽእኖ” ደርሶበት እንደማያውቅም ገልጸዋል።
    የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ይህን ያሉት፤ የሰብአዊ መብት ተቋማትን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት ለሰነዘሩት ትችት በሰጡት ምላሽ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ትላንት ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 በተካሄደ የፓርላማ ስብሰባ ላይ የሰብአዊ መብት ተቋማትን እና አሰራራቸውን “መፈተሽ” እንደሚያስፈልግ ተናግረው ነበር።
    አብይ በዚሁ ንግግራቸው የሰብአዊ መብት ተቋማት ከሌሎች ሀገራት እና ፍላጎቶች ተጽእኖ “ነጻ መሆን” እንደሚገባቸው አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እኛ ደመወዝ የማንከፍለው፣ ሌሎች ኃይሎች የቀጠሩት፣ ለሌሎች ኃይሎች ሪፖርት የሚያደርግ ተቋም ኢትዮጵያ ውስጥ ከፈቀድን፤ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለእናንተ መተው ነው” ሲሉም የመገመቱን ድርሻ ለፓርላማ አባላት ትተው ነበር።(ኢትዮጲያ ኢንሳይደር)
    ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
    -------------------------------------------------------------------------------------------
    የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
    ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...​
    ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
    ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
    ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
    ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider

ความคิดเห็น •