DW Amharic የጥር 17 ቀን 2017 የዓለም ዜና
ฝัง
- เผยแพร่เมื่อ 7 ก.พ. 2025
- የጥር 17 ቀን 2017 የዓለም ዜና
• የትግራይ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ከፍተኛ የትግራይ ወታደራዊ መኮንኖች የሰጡትን መግለጫ እና የያዙት አቋም “በመደገፍም ሆነ በመቃወም” ሰልፍ ማካሔድ እንደማይቻል አስታወቀ። በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ማይጨው እና መኾኒ ከተሞች ጨምሮ ሌሎች ወረዳዎች የአስተዳደር አካላት የጠሩት እና የወታደራዊ መኮንኖቹን ውሳኔ የሚቃወም ሰልፍ መደረጉ የትግራይ ኮምዩንኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
• ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል 100 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለታንዛኒያ የምትሸጥበት ሥምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። “የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች” ከጸደቀ በኋላ ከመጪው ሚያዝያ 2017 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
• በሱዳን ዳርፉር ግዛት ኤል-ፋሽር በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በሰው አልባ አውሮፕላን በተፈጸመ ጥቃት 30 ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸውን የሕክምና የመረጃ ምንጮች ዛሬ ቅዳሜ ተናገሩ።
• ሦስት የደቡብ አፍሪካ ሰላም አስከባሪዎች በዴሞክራቲት ሪፐብሊክ ኮንጎ ተገደሉ። በኮንጎ ጦር እና በርዋንዳ የሚደገፈው ኤም23 የተባለ አማጺ መካከል ከፍተኛ ውጊያ እየተደረገ ነው።
• በጋዛ የተኩስ አቁም ሥምምነት መሠረት እስራኤል 200 ፍልስጤማውያን እስረኞችን፤ ሐማስ 4 ታጋቾችን ዛሬ ቅዳሜ ለቀቁ።
ሰላም ሰላም።
❤🎉❤❤❤❤
hi dw