የመንግስቱ ፕሮቶኮል 2016 ክፍል 5

แชร์
ฝัง
  • เผยแพร่เมื่อ 10 ก.พ. 2025
  • የኪዳን ፈተናዎች እና ታማኝነት
    እግዚአብሔር በህይወትህ የተናገረህ ነገር ተፈጻሚነት የሚወሰነው በገባከው ኪዳን እና ለገባከው ኪዳን ባለክ ታማኝነት ነው
    ሰው ኪዳን አፍራሽ የሚሆነው ፍርዱን ሳይረዳ ሲቀር ነው
    እግዚአብሔር በይቅርታ ለሚመለሱ ቤዛ የሚሆንን ይሰጣል እንጂ በፍጹም የኪዳንን ፍርድ ከማስፈጸም ወደኋላ አይልም!
    ሁሉም ኪዳኖች የውል ወሰን አላቸው! ኪዳን ከወሰኑ ውጪ አይሰራም!
    👉ማቴዎስ 20
    📍እግዚአብሔር የሚከፍልህ የታማኝነት ዋጋ እንጂ የሰራህበትን አይደለም!
    ኪዳን በሁለት ነገሮች ይፈተናል
    1 ኪዳን ከሰው ወይም ከሰይጣን በሚመጣ ክፉ ፈተና (Temptation) ይፈተናል
    2 ኪዳን ከእግዚአብሔር በሚመጣ የመመዘኛ ፈተና (Test) ይፈተናል
    ኪዳን ተስፋ አለው! የሚያመጣው በረከት አለው!
    ጠላትም የሚመጣውን በረከት በማሰብ የኪዳን ሰዎችን ይቃወማል!
    📌እግዚአብሔር የሰጠህ ህብረት ወይም ግንኙነት የሚያመጣው በረከት ለጠላት ክፉ ዜና ነው! ስለዚህ ለእግዚአብሔር ደጅ የሚሆነውን ኪዳን ለማፍረስ ይሰራል!
    ኪዳን እስካልፈረሰ ድረስ ስኬትህ የተረጋገጠ ነው ስለዚህም ክፉ ይፈትነዋል! በመርሳት ፣ በአመንዝራነት እና በከሃዲነት ይፈተናል
    😶‍🌫️የመርሳት ፈተና ሰዎች ኪዳንን እንዲዘነጉ ብሎም እንዲያፈርሱ ያደርጋቸዋል
    አንድ ሰው ኪዳን ገብቶ መጓዝ ሲጀምር የኪዳኑን በረከቶች በህይወቱ ማየት ይጀምራል ነገር ግን ሲቆይ በኪዳኑ ምክኒያት እንዳገኛቸው ረስቶ ሲያፈርሰው ይችላል በዚያን ጊዜ እነዚያን በረከቶች አንድ በአንድ ከህይወቱ ማጣት ይጀምራል!
    📌እግዚአብሔር በኪዳን ውስጥ የሰጠውን በረከት ሊጠብቅ የሚችለው ኪዳኑ እስከጸና ብቻ ነው!
    👉 ሆሴዕ 2 እና ዘፍጥረት 17
    ኪዳን ሲታደስ ክብርህ ይታደሳል!
    📌አመንዝራነት ኪዳን ከተገባለት አካል ውጪ የሚደረግ ሌላ ውል ወይም ስምምነት ሲፈጠር ማለት ነው
    አለምን መውደድ ከእግዚአብሔርን ጋር ያለን ኪዳን በሌላ መቀየር መንፈሳዊ አመንዝራነት ነው
    "አመንዝሮች ሆይ፤ ከዓለም ጋር ወዳጅነት ከእግዚአብሔር ጋር ጠላትነት መሆኑን አታውቁምን? ስለዚህ የዓለም ወዳጅ መሆን የሚፈልግ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኗል።" 📖ያዕቆብ 4:4

ความคิดเห็น •